የእኛ ሰው በአሜሪካ _በነቢይ መኮንን _ኒውዮርክ ውስጥ (መነበብ የሚገባው እውነት)

April 22, 2010
ኒውዮርክ ውስጥ ::

ኒውዮርክ ከሁሉ ነገርዋ ጎልቶ የሚታይባት የመጤ ዜጋ መብዛት ነው ::"ሁሉን አቅፍ ባይ ናት " እንደመርካቶ :: አበሻም በርካታ አላት ::አብረውኝ የጋዜጣ ህትመት ፕሮግራም ከሚከታተሉት ጓደኞቼ መካከል ከፓኪስታንና ከሲሪላንካ ከመጡት ወዳጆቼ ጋር ኒውዮርክ ጉራንጉር ድረስ ሄደናል :: የኒውዮርክ ገበያ አስገራሚ ነው :: እንደፓሪስ እጅግ ውድ "የሚታይ እንጂ የማይበላ ፍሬ " የሚባለውን አይነት ዋጋው ንቅንቅ የማይል እቃ አለ :: በአንጻሩ እንደመርካቶ 70 ዶላር የተባለውን እቃ ተከራክሮ 23 ዶላር መግዛት የሚቻልበትም ሱቅ አለ ::

አንድ ልቤን የነካኝና ያሳዘነኝ ነገር ግን በተዘዋወርንበት ስፍራዎች ፓኪስታኑ ጓደኛዬ የፓኪስታን ማህበረሰብ አገኘ :: እንደ ጉድ የሚነግዱ ታታሪ ፓኪስታኖች ያሉበት :: ሲሪላንካዊው ጓደኛዬም ተርብ ተርብ የሆኑ የስራ ሰዎች የሆኑ ሲሪላንካውያን ተደራጅተው የልብስ የጫማ ስፌት የአሮጌ ቴፕ እደሳ ንግድ ያጡዋጡዋፉበት ቦታ ወሰደኝ :: "ኢትዮጵያውያንስ የት ነው ስራ የሚሰሩት ?ኮሚኒት አላቸው አደል ?" ብለው ቢጠይቁኝ አይኔ ፈጠጠ :: ቅስሜ ተቀጨ :: ከዛ ሁሉ በሺዎች ከሚቆጠር እኔ ካየሁት አበሻ ተደራጅቶ ስራ የሚሰራ የለም እኔ እስከማውቀው ድረስ :: ተነጣጥሎ ተነጣጥሎ የቀን ሞያተኛነት ስራውን ሊሰራ ይበታተናል :እንደሚታወቀው የሚሰባሰበውም ለወሬ ብቻ ነው - የፈረደበት የአበሻ ሬስቶራንት ውስጥ :: የጉዞ ጓደኞቼን የትም ልወስዳቸው ባለመቻሌ እዛው አበሻ ሬስቶራንት ወስጄ ራት ጋበዝኩዋቸው :: ወርቁ ቢጠፋ ሚዛኑ አይጥፋ ነው መቼስ :: ወደ ሆቴሌ ስመለስ ገና ኒውዮርክ እንደገባሁ ደውዬ መልእክት ትቼላቸው ከነበሩ ወዳጆቼ መካከል መልስ የሰጠኝ የአንዲት አክስቴ ልጅ ባልና ኢብሳ ጉተማ የኦ ኤል ኤፍ አመራር አባል ይገኙበታል ለሁሉም የመልስ ምት ደወልኩኝ :: አቶ ኢብሳን ለጊዜው አላገኘሁትም መልእክት ተውኩለት ::

የአክስቴን ልጅ ባል አገኘሁት ::
አማቼ ልበለውና ከአማቼ ጋር ማታውኑ ተቃጠርን :: በአንድ የአበሻ ሬስቶራንት ውስጥም ተገናኘን ::
"እዚህ ጥሩ ጠጅ ይሰራሉ እስቲ ሞክረው :: የአሜሪካን ጠጅ ቀምሰኸዋል ?"
"አረ አልቀመስኩትም !" አልኩት ::
"በል አሁን ቅመሰው :: ሄደህ ለእነ ይገባዋል ጠጅ ቤት ለእነ ቀስቶ : ለእነ ጎንደር ጠጅ ቤት ትነግርልናለህ !"
"ይሄን ሁሉ የጠጅ ቤት ስም ማስታወስህ ይገርማል ::"
"ሌላ ምን ስራ አለን :: አሜሪካን ቁጭ ብለን በትዝታ ነውኮ የምንኖረው ትናንትን እየከለስን "
ጠጁ ታዘዘና መጣ :: ዘይት ይመስላል - ጥልል ያለ መነን ዘይት !! በጠርሙስ ነው የሚሸጠው አንዱ 10 ዶላር ያወጣል :: ገና ለማጣጣም ሁለት ስጎነጭ አናቴ ላይ ወጣ :: ማስከሩ ነው እንጂ የአገሬን ጠጅ ጠጅ አይልም :: ማሩ ከሀገራችን ነው የሚመጣው ::ስኳሩም ያው ስኳር ነው :: ታድያ ምን እንዲህ ጣእሙን አጠፋው ? ከውሀው ይሆናል አልኩና እንደ እንጀራው አስታመምኩት :: ከዚያ ስለ ሀገር ቤት ጠየቀኝ :: ብዙ አመት በአሜሪካ እንደቆየ አስረዳኝ :: እንደብዙ አበሻ ማንሀታን የጥቁሮች መንደር አካባቢ እንደሚኖር :
ሌሎችም ብዙ ወደ ክዊንስና ብሮንክስ እንደሚኖሩ አስረዳኝ ::
"ለመሆኑ ኑሮ እንዴት ነው አልኩት ?"
"ጥሩ ነው ምንም አይልም " መለሰልኝ ::
"እዚህ ብዙ የአበሻ ሬስቶራንት አለ እንዴ ?"
"እንደዲሲ አይሆንም እንጂ አለ "
"ምንድነው እንደዲሲ እንዳይሆን ያደረገው ?ብዙ አበሻ የለም እንዴ ?"
"እንደ ዲሲ አይሆንም :: እዚህ የሌለ አይነት ዜጋ የለም :: ጥቁር ነጭ ቡናማ ቢጫ ቀለም ያለው .... የሰው ዘር የተባለ ሁሉ አለ :: አበሻም አለ ግን እንደ ዲሲ በዞርክበት የምታገኘው አይነት አይደለም ::"
"ኑሮውስ እንዴት ነው ?"
"አወዳድረን ስናየው ውድ ነው !"
አንድ ጥያቄ ለመጠየቅ ስፈራ ስቸር ቆይቼ
"ለመሆኑ ከኢትዮጵያ ከመጣህ ተምረሀል ?ብዙዎቹ አበሾች ስለትምህርት ሳነሳ ወይ ይከፋቸዋል መማር ምን ያደርጋል :ተምረህም ኩሊ ነው የምትሆነው የሚል አመለካከት ነው ያላቸው " አልኩት ::
"እኔ መጀመሪያ ወደ አሜሪካ ሳይሆን ወደ አውሮፓ ነው የተሻገርኩት :: እዛ ማስተርሴን ሰራሁ :: እኔ ያለትምህርት የትም ይደረሳል ብዬ አላምንም :: ከሀገሬ ወጥቼ በስደት መከራን የማየውም ለመማር ብዬ ነው ::"
"ተባርክ !" አልኩት በሆዴ ::
"ከዚያስ አሜሪካን መጥተህ እንዴት ሆንክ ?"
"!አሜሪካና አውሮፓ በጣም ይለያያል :: እዚያ የማህበራዊ ዋስትና ገንዘብ ይሰጥሀል :: እዚህ ዱዲ ቀይ ድንቡሎ የሚሰጥህ የለም :: አፈር ግጠህ ዶላርህን ታጠራቅማለህ :: በቃ ትኖራለህ :: አውሮፓ ከፈለክ ዝም ብዬ ልደንስ ካልክ ተኝተህ ትበላለህ :: ስደተኛነትህን የምታስታውስህን ያህል ጥቂት ገንዘብ ይሰጡሀል ከወር ወር አብቃቅተህ እስዋን እየቆረጠምክ ለጥ ልትል ትችላለህ :: እዚህ እንዳልኩህ እስከ መጨረሻዋ የላብ ጠብታ ሰርተህ ደም ተፍተህ ነው መኖር የምትችለው :: ከለፋህ ጥሩ ትኖራለህ ::"
"ካልለፋህስ ?"
"ተጨንቀህ ተደብረህ ትሞታለህ "
"ብትሰራስ ጭንቀት ይቀርልሀል ማለት ነው ?"
"አየህ የጭንቀት ጫና እኛም ላይ ነጩም ላይ አለ :: እርግጥ የኛ ይብሳል ::"
"ለምን ?"
"እኛ "አይደንቲቲ ክራይሲስ "(የማንነት ረሀብ ) አለብን :: እትዮጵያዊ ነን እንዳንል እንደፈረንጁ ካልሆን እያልን መከራ እናያለን :: ፈረንጅ እንዳንሆን በጭራሽ የአበሻ ልጅነታችን ይጎትተናል ::"
"እስቲ የአውሮፓውን የማንነት ረሀብና የዚህ አገሩን አወዳድርልኝ "
"ይገርምሀል አውሮፓ ነጭ ነጭ ነው ጥቁር ጥቁር ነው ::"
"እኔም አውሮፓን አይቸዋለሁ :: እንዳልከው ነጭ ነጭ ነው :: ጥቁርነትህን ቶሎ ይሰማሀል :: እንዲሰማህ እያደረጉህ ነው ? ወይስ አንተም በጥቁርነትህ ትንሽ የዘረኝነት ስሜት አያጣህም ?"
"ኢን ዌይ ልክ ነህ :: እኛም ነጩን ስናይ ወዲያው ጥቁርነታችን ፍጥጥ ብሎ ይወጣል :: እኛ እንግዲህ በአረብና በሌላው ጥቁር አፍሪካዊ መካከል ነን የሚል የቡና አይነትነት የበላይነት (የምርጥነት ) ስሜት በውስጣችን አለ :: ነጩ አጠገባችን ሲኖር ግን ወዲያው ባልጩት መስለን ቁጭ እንላለን :: ልባችንን ጭምር ጥቁርቁር እናደርጋለን :: ስለዚህ ነጩ ነጭነቱ የሚናገርበት አፍ ብቻ አይደለም ያለው :: ቴክኖሎጂ አለው :: ትላልቅ ቡና ቤቶችና ሆቴሎች አሉት :: እነዚህ ጥቁርነትህን ይነግሩሀል :: መቶ ግዜ ኪስህን ብትቡዋጥጥም የምታወጣው ገንዘብ በጭራሽ የማይደፍራቸው ውድ ውድ ቦታዎች አሉ :: የቡና ቤቶቹ ቦዮች ሳይቀሩ እንዴት እንደሚንቁህ ታያለህ :: በግልጽ !አውሮፓ በግልጽ ስደተኛ ነህ ይሉሀል :: ቁርጥህን አውቀህ ቁጭ ትላለህ !"
"አሜሪካስ ስደተኛነትህ እንዳይታወቅህ ያደርጋል እንዴ ?"
"በጭራሽ :: አሜሪካንም ያሳውቅሀል :: ግን እንዳሳወቀህ አያሳውቅህም በአብዛኛው ሽፋን አለው "
"እንዴት ቢያንስ አንተ ራስህ ጥቁርነትህን ስደተኛነትህ ይታወቅህ የለም እንዴ ?"
"አንተማ አዎ :: ግን እንግሊዝ ጀርመን ፈረንሳይ ገና ሲያይህ ሲቀፈው ይታወቅበታል :: እሱ የገባበት ሆቴል እንዳትገባ ይፈልጋል :: እሱ የሚከፍለውን ያህል ስትከፍል ቢያይ ደሙ ይፈላል ::
አሜሪካ እሱ የሚከፍለውን ያህል ስትከፍል ቢያይ ገንዘቡን ወደ አገርህ ይዘሀት እንዳልሄድክ በማየት ይደሰታል :: አሜሪካ ውስጥ ጨፍር ደንስ እበድ ጉዳዩ አይደለም :: ናይት ክለቡን ጭፈራ ቤቱን ጌቶውን ሐርለሙን ሐሺሹን ራቁት ዳንሱን መደሰቻ ቤቱን ሁሉ ነው የሚያመቻችልህ :: ከሀገሩ ቤሳ ቤስቲን ይዘህ እንዳትወጣ ነው :: ጉልበትህን እንጂ አንተን አይፈልግህም ::ግን እንደደረጃህ (ከቀናህም ከሰው በላይ )እየቀበጥክ እየዘለልክ እንድትኖር ይፈቅድልሀል ::ልክህን ያውቀዋል :: ግን ልክህን የሚያሰምርልህ በሆዱ ነው : ሽሽግ ነው የምልህ ለዚህ ነው ::
"እንዳይታወቅ ያደርጋል ማለት ነው አውቆ ?"
"... ኖት ኢን ዌይ ... ምን መሰለህ ማንም አሜሪካዊ ሲስተሙ -ስርአቱ አንተን ልክ እንደሚያገባለት ያውቃል :: ለምሳሌ ብታድግ ብታድግ ምን ችሎታ ቢኖርህ ከሱ እኩል እንድትሆን አይፈቅድም ስርአቱ :: ያግድሀል :: ቢሮ ገብተህ በወግ ተቀምጠህ ከእሱ እኩል ኮርተህ ስራ የመስራት እድል የሚያጋጥምህ ከስንት ሺህ አንድ ብቻ እንደሆነ አሳምሮ ያውቃል :: የጉልበት ስራውን ግን የሚከለክልህ የለም :: እሱ ሚልዮን ዶላር ለምን አታፈራም አይመቀኝብህም ::አንተ የተፈጠርከው ለዚህ ነው ማለቱ ነው ! አሜሪካ በድንበር ተሰደህና በቦሌላ በባሌ ጉልበትህን ይዘህላት እንደመጣህ ስለምታውቅ እኔ የአለም ልጆች እናት ነኝ :: ሁሉም እኔ ውስጥ ተስማምተው ይኖራሉ ትልሀለች :: ዶላር ሳይሆን ጉልበትህ ይዘህ እንደመጣህ አሳምራ ታውቃለች :: ብዙ ለፈለፍኩብህ .... ብሶቴን አንተ ላይ የማራግፍ መሰለኝ ? እስቲ አንተ ተጫወት ነቢይ ?"
"በጣም ተስማምቶኛል :: ቀጥል ግድ የለህም :: አስተያየትህም ሆነ የተሰማህ ስሜት ዲሲ ካጋጠሙኝ አበሾች ይለያል :: ....ስለ አበሾች የአእምሮ ጭንቀት ጫና ስታነሳ ምን ትዝ አለኝ መሰለህ ? አዲስ አበባ መስቀል አደባባይ "ቴዲ አፍሮ " የተባለው ዝነኛ ወጣት ዘፋኝ ይዘፍናል ተብሎ በሺዎች የሚቆጠር ተመልካች ይታደምልሀል :: በመሀል ምን እናያለን የቀይ መስቀል መኪና :: ይህ ደግሞ ለምን መጣ ? ብዬ አንዱን ወጣት ጠየኩት :: "ማይክል ጃክሰን ሲዘፍን አድማጩ "ፌንት " አድርጎ ሲወድቅ : ሌላም ፈረንጅ ሲወድቅ አይተው የቴዲ አድናቂዎችም ፌንት አድርገው እንዳይወድቁ ተፈርቶ ነዋ ! አበሻኮ ፌንት አድርጎ ወድቆ አያውቅም :: ! ስትሬስ ምናምን በጭራሽ አይነካውም ! አለና በሳቅ ገደለን ::....

"አሁን ትምህርትህ ምን ደረሰ ?"
"አሁንማ በህክምና ዶክትሬቴን ጨርሻለሁ ::"
" ሀኪም ነሀ ! የት ትሰራለህ ?
"እሱ ነው ጉዱ !"
"እንዴት ?"
"አሜሪካን ሀገር የህክምና ዶክትሬትህን ትይዛለህ እንጂ በቀጥታ ሀኪም ትሆናለህ ማለት አይደለም ::"
"አልገባኝም :: ስራ በቀላሉ አይገኝም ?... ማለቴ አይቀጥሩህም ወይስ ...."
"ዌል .... እንደሱ ነው ማለትም ይቻላል :: ግን ....
አሁን ግራ ገባኝ :: እነዚህ አበሾች ስራ ሲደርሱ አፋቸውን የሚይዛቸው ነገር አለ !::
"ምንድነው ችግሩ ?በተማርከው ትምህርት ስራ መስራት ክልክል ነው እንዴ ?
"አረ በጭራሽ ?"
"ታዲያ ... አንተ ለምሳሌ አሁን ምን ትሰራለህ ?"
"ይሄውልህ ነቢይ :: ከምኖርበት ከተማ የምሰራበት ቦታ ድረስ የአንድ ሰአት ተኩል ያህል ጉዞ ነው :: እዚያ ድረስ እየነዳሁ ሄጄ ነው ስራ ስሰራ ውዬ የምመለሰው :: ትምህርቴን ከጨረስኩ ወደ 3 አመት ገደማ ሆኖኛል :: እየተማርኩ እያለሁ ሆቴል ማስተናገድም ፓርክ ላይ መኪና ማስተናገድም የጉልበት ስራ አንዳንዴ ሳገኝ ደግሞ /ቤት ውስጥ ለዶክተሮቹ ረዳትነትም እሰራ ነበር ::"
"አሁንስ ?"
"አሁን የምሰራበት እንዳልኩህ አንድ ሰአት ተኩል የመኪና ጉዞ ቦሀላ የሚገኝ አንድ ሆስፒታል አለ ...."
"!አንተ ታድለሀል ቢያንስ በተማርከው ትምህርት ነው ስራ የምትሰራው !...."
"ነውም አይደለምም "
"ለምን .... ነው እንጂ !"
"አየህ አሁን ለጊዜው የምሰራው በሽተኞች ወደ ሆስፒታሉ ሲመጡ ተራ ማስያዝ ነው :: ማሰለፍ በለው ...."
እኔ ለትንሽ ግዜ ጸጥ አልኩኝ :: ትንፋሽ ያጠረኝም መሰለኝ ::
"ለመሆኑ በሽተኛ ስታሰልፍ መዋሉን ህሊናህ እንዴት ተቀበለው ?" አልኩት ከአፍታ ረፍት ቦሀላ ::
"ምን ታደርገዋለህ ! ባትቀበል የት ትደርሳለህ ? አየህ ቀስ ቀስ እያልክ ወደ ሙያህ እየተጠጋህ ትሄዳለህ :: ላትደርስም ትችላለህ :: እንደውም አብዛኛውን ጊዜ Asymptotic graph አይነት ነው (በሂሳብ /ርት መስመሩ ይጠጋል እንጂ አይነካም የሚባለውን ግራፍ አይነት ማለቱ ነው )
 

የእኛ ሰው በአሜሪካ በነቢይ መኮንን _የፈረንሳይ አጋጣሚ

April 22, 2010
"ፈረንሳይ ሀገር ያጋጠመኝን አንድ ነገር ላጫውታቹ " አልኩ :: ሁሉም ከየሀሳብ ጎጆዋቸው እየወጡ "እሺ " በሚል አይን አዩኝ ::
"ፈረንሳይ አገር አንድ ሎጋ ወጣት ልጅ ምን ልታደርግ ወደ ኢትዮጵያ ትመለሳለህ ? እያለ አላስቆም አላስቀምጥ አለኝ :: በመጨረሻም እስቲ ቤትህን አሳየኝ ? ብዬ በተራዬ አላ...

Continue reading...
 

የእኛ ሰው በአሜሪካ በነቢይ መኮንን .... ኒውዮርክ ውስጥ ነው

April 22, 2010
ወደ ኒውዮርክ ልንሄድ በዋዜማው እንደለመድኩት ከአንድ አራት የዲሲ ነዋሪ አበሾች ጋር ለማምሸት ቀጠሮ ይዤ ነበር :: እነሱም የአገር ቤት ወሬ ናፍቀዋል ::እኔም የነሱን አንዋንዋርና ህይወት ለማወቅ ጉዋጉቻለሁ :: ከቅርብ አመታት ወዲህ በዲቪ ወደ አሜሪካ ስለሚወጣ የአገራችን ሰው ጨዋታ ተ...
Continue reading...
 

የኛ ሰው በአሜሪካ በነቢይ መኮንን ገጽ 16...

April 22, 2010
ዋሺንግተን ዲሲ ዱከም ሬስቶራንት ውስጥ ነው ውስጥ ነው ::

ለምንድነው የሚሰሩትን ስራ ለመግለጽ የማይፈልጉት ? ለምንድነው መማር የሁሉም ፍላጎት ያልሆነው ?ለምንድነው ከኢትዮጵያ በእንግድነት የመጣ ሰው እዚያ እንዲቀር የሚፈልጉት ? የት ሲሰሩ ውለው ነው ማታ ማታ አበሻ ሬስቶራንት የሚ...

Continue reading...
 

Kibebew Geda comedy - Welaj

April 22, 2010

Continue reading...
 

If you are unable to see amharic fonts please download most common amharic fonts in downloads catagory or click here.

Make a Free Website with Yola.