የእኛ ሰው በአሜሪካ በነቢይ መኮንን _የፈረንሳይ አጋጣሚ

Posted by Basha BIRU on Thursday, April 22, 2010 Under: Litrature ... Fiction/others
"ፈረንሳይ ሀገር ያጋጠመኝን አንድ ነገር ላጫውታቹ " አልኩ :: ሁሉም ከየሀሳብ ጎጆዋቸው እየወጡ "እሺ " በሚል አይን አዩኝ ::
"ፈረንሳይ አገር አንድ ሎጋ ወጣት ልጅ ምን ልታደርግ ወደ ኢትዮጵያ ትመለሳለህ ? እያለ አላስቆም አላስቀምጥ አለኝ :: በመጨረሻም እስቲ ቤትህን አሳየኝ ? ብዬ በተራዬ አላስቆም አላስቀምጥ አልኩት :: ሄድን :: ያጋጠመኝ ነገር እጢዬን ዱብ ነው ያደረገው :: ይሄ 24 አመት ወጣት በአይን ግምት 58 አመት የሚሆናት ፈረንሳዊት አሮጊት አግብቶ ነው የተቀመጠው ::ከፈረንሳይ እንዳይወጣ ጭምር ከአሮጊትዋ ጋር በፊርማ ታስሮ ነው የሚኖረው :: የሚገርመው ለምን ይህ ሊሆን ቻለ ? ብዬ ስሜት በማይነካ ትሁት አማርኛ ጠየኩት ::
"ጠርዘው ወደ ሀገሬ ሊመልሱኝ ሲሉ ይህን ዘዴ አገኘሁ አለኝ ::
"እሺ እንዴት ትግባባላቹ ? እንዴት ማች ታደርጋላቹ ? ብዬ ጠየኩት ::
ብዙ አፈረ ::ብዙ አቀረቀረ :: የሚገርማቹ የባልና ሚስቱ ኑሮዋቸው ሀዘን ላይ ነው የጣለኝ :: የሱ ሀላፊነት -ጉዋደኞችዋ ማለትም እስከ 65 አመት ያሉ አሮጊቶች ባልንጀሮቹዋ ሲመጡ ሻይ ማፍላት ቡና ማፍላት ሲወጡ እጃቸውን ይዞ መንገድ ማሻገር የየሳምንቱ የብዙ ቀናት ስራው ነው ::
የመጣሁት እውነቱን ለመንገርና ለመናደድ ነበር :: ይሄን የመከራ ኑሮ እየኖርክ ለምን አገርህ አትመለስም አልኩኝ ብዬ ለመቆጣት ነበር :: ጉዳዩ ግን የተገላቢጦሽ ሆነ ::በሁኔታው ልቤ በጣም ተነክትዋል :: "አሳዝነኸኛል " አልኩት አሁንም የልቤን መሳሳትና የአንጀቴን መንሰቅሰቅ በሚያሳይ ስስ አንደበት :: አይኖቼ ላይ እንባ ተንቸረፈፈ :: በኑሮው እንደማይደሰት ለማወቅ ምንም መናገር አላስፈለገውም :: አላስፈለገኝምም :: ለመሆኑ እንደው በሆነ አጋጣሚ እንዴት እየኖርክ እንደሆነ ለቤተሰቦችህ ወይም ለቅርብ ጓደኛህ ወደ ኢትዮጵያ ደብዳቤ ጽፈህ ታውቃለህ ?"
"በጭራሽ "
"ለምን ?"
"ይሄ ማፈሪያ ነገር ምኑ ይጻፋል ?"
"ብትጽፈው ጥሩ ነበር "
"ተወው ብትፈልግ አንተ ጻፈው :: ፈቃዱን ሰጥቸሀለሁ " አለኝ ከዚያች ቀን ወዲህ ስለ ከአገር መቅረት አውርቶኝ አያውቅም ::

In : Litrature ... Fiction/others 


Tags: life in america  life in france  ኢትዮጵያዊ በፈረንሳይ 

If you are unable to see amharic fonts please download most common amharic fonts in downloads catagory or click here.

Make a Free Website with Yola.